የማህበራዊ እና ስሜታዊ ትምህርት (SEL) ማጣሪያ

Arlington Public Schools (APS፣ አርሊንግተን የህዝብ ትምህርት ቤቶች) ከክፍል 3-12 ላሉ ተማሪዎችን የማህበራዊ-ስሜታዊ አለም አቀፋዊ ማጣሪያ ለማካሄድ ከ Panoram ጋር ውል ተፈራርመናል። የዚህ ዳሰሳ ጥናት አላማ APS የሁሉንም ተማሪዎች ማህበራዊ-ስሜታዊ እና የቀለም ትምህርት ፍላጎቶችን እንዲለይ፣ ሪፖርት እንዲያደርግ እና እንዲፈታ ለመርዳት ነው። ትምህርት ቤቶች በእያንዳንዱ ክፍል ለማጣራት የተለየ ቀን ቢያስቀምጡም እንኳን ተማሪዎች ከማርች 21 ጀምሮ እስከ ኤፕሪል 8 ባለው የሶስት ሳምንት ክፍተት ውስጥ አንድ ጊዜ በዚህ የኦንላይን ዳሰሳ ጥናት ውስጥ ይሳተፋሉ።

የ Panorama SEL አለም አቀፋዊ ማጣሪያ ግላዊ እውቀት፣ ራስን መቆጣጠር፣ ማህበራዊ እውቀት፣ የግንኙነት ክህሎቶችን እና በሀላፊነት የሚደረግ ውሳኔ አሰጣጥን ከሚያካትቱ አምስት የ SEL ችሎታዎች እና ከ Collaborative for Academic, Social, and Emotional Learning (CASEL፣ የቀለም ትምህርት፣ ማህበራዊ እና ስሜታዊ ትምህርት ትብብር) ጋር ይስማማል። የ SEL ማጣሪያው ተማሪዎች የራሳቸው ክህሎቶች እና ተሞክሮዎች ላይ እንዲሁም የባለቤትነት ስሜታቸው፣ ስለ ትምህርት ቤቱ አካባቢ ላይ ያላቸው እና ስሜታቸው ላይ እንዲያንጸባርቁ እንዲሁም ሪፖርት እንዲያደረጉ ያስችላቸዋል። እነዚህ ምክንያቶች ለአዎንታዊ የቀለም ትምህርት፣ ማህበራዊ እና ስሜታዊ ስኬት ወሳኝ ናቸው።

የ SEL ማጣሪያ ውሂብ 1) የግላዊ፣ የክፍል፣ የምህርት ቤት፣ እና የዲስትሪክት ፍላጎቶች ላይ ከፍ ያለ አረዳድን ያቀርባል፤ 2) ተጨማሪ ጣልቃ ገብነቶች ወይም ድጋፎችን ሊፈልጉ ወይም ከእነዚህ ሊጠቀሙ የሚችሉ ተማሪዎችን ይለያል፤ 3) በጊዜ ሂደት መሻሻል እና ለውጥን ይቆጣጠራል፤ 4) ለ SEL ፕሮግራም ውሳኔዎች እና በየደረጃው ላሉ የድጋፍ ስርዓቶች መረጃ ለመስጠቅ ውሂብ ያቀርባል፤ 5) ፍትሐዊነትን ያሰፍናል፤ እና 6) አለም አቀፋዊ የ SEL ድጋፎችን ያሳውቃል።

የማጣሪያው ውሂብ ህጋዊ ትምህርታዊ ፍላጎቶች ላላቸው አስተማሪዎች፣ አስተዳዳሪዎች እና ሰራተኞች ብቻ ይገኛል። ውጤቶቹ ለእነዚህ ሰዎች ብቻ ተገኚ በሆኑ ጥብቅ ፋይሎች እና ዳታቤዞች ውስጥ ይቀመጣሉ። ወላጆች እና አሳዳጊዎች እያንዳንዱን የምዘና ክፍተት ተከትሎ የተማሪዎቻቸውን የማጣሪያ ውጤቶች መሰረት በማድረግ ግላዊ ሪፖርት ይቀበላሉ። የትምህርት ቤት ሰራተኞች በታቀደው ድጋፍ ላይ ከቤተሰቦች ጋር ስለ ውጤቶች ለመነጋገር ይገኛሉ።

ልጅዎ በ SEL ማጣሪያው ውስጥ እንዲሳተፍ የማይፈልጉ ከሆነ፣ በኤሌክትሮኒካል መንገድ እንዲሞሉ እና እንዲያስገቡ የሚያስችልዎን ተከታዩን የፍቃድ መንሻ ቅጽ ጠቅ በማድረግ ቅጹን በሰኞ፣ ፌብ. 14 እባክዎ ይሙሉ፦ https://survey.k12insight.com/r/SEL

ስለ የ SEL አለም አቀፋዊ ማጣሪያ የበለጠ ለማወቅ፣ የ APS SEL አልም አቀፋዊ የማጣሪያ ድረገጽን  የ Panorama የማህበራዊ ስሜታዊ ጥምሕርጥ የዳሰሳ ጥናት ላይ እንዲጎበኙን እንጋብዝዎታለን። ተጨማሪ ጥያቄዎች ወይም ስጋቶች ካልዎት፣ እባክዎ የተማሪውን የትምህርት ቤት አማካሪ ያነጋግሩ።