Full Menu
Search

የክትባት አስፈላጊነት ማሳወቂያ

በጋውን በጉጉት እየተጠባበቁ ሳለ ለአዲሱ ለትምህርት ዘመኑ ዝግጁ እንዲሆኑ ለማስቻል የክትባቶችንና የአካላዊ ምርመራዎችን በእቅዶችዎ ውስጥ ማካተትዎን ያረጋግጡ!የቨርጂኒያ ስቴት (የቨርጂኒያ ሕግ § 32.1-46.A.4) በስቴቱ ውስጥ በግል ወይም በመንግስት ትምህርት ቤቶች የሚመዘገቡ ተማሪዎች በሙሉ አሁን ካለው የክትባት ተግባራት ላይ አማካሪ ኮሚቴ (ACIP) ምክሮች ጋር የተጣጣሙ ሆነው እንዲቀጥሉ ይፈልጋል፡፡ ተማሪዎች በአካል ትምህርት ቤት ተገኝተው ለመማር በመጀመሪያ የትምህርት ቀን ዝቅተኛውን የጤና መግቢያ መስፈርቶችን ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡ በሁሉም የትምህርት ቤት የክትባት መግቢያ መስፈርቶች፣ አጋዥ ተደጋግመው የሚነሱ ጥያቄዎችንና መመዝገብ ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች መረጃ በቨርጂኒያ የጤና መምሪያ ድህረ ገጽ፡ የትምህርት ቤት መስፈርቶች – ክትባቶች (virginia.gov) ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡ ለሁሉም አዲስ ለሚመዘገቡ ተማሪዎች እንዲያሟሉ ከሚጠበቁባቸው መስፈርቶች በተጨማሪ፡

  • ወደ መዋእለ ሕጻናትና አንደኛ ክፍል የሚገቡ ተማሪዎች የሄፐታይተስ ክትባት (HAV) የተከፋፈሉ ሁለት ክትባቶችን በትክክል ስለመከተባቸው የሚያሳይ ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው፡፡ የመጀመሪያው ክትባት በ 12 ወር ወይም ከዚያ በላይ በሆነ እድሜ መሰጠት አለበት፡፡
  • 7 ክፍል የሚገቡ ተማሪዎች አንድ ቴታነስ ዲፍቴሪያና ፐርቱሲስ ክትባት (Tdap) ማበረታቻ በ 7 አመት ወይም ከዚያ በኋላ የሚሰጥ ሲሆን እንዲሁም በ 10 አመት ወይም ከዚያ በኋላ የሚሰጠው የማኒንጎኮካል ኮንጁጌት ክትባት (MenACWY) የመጀመሪያ ክትባት ስለመውሰዳቸው ማስረጃ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የቨርጂኒያ የጤና ጥበቃ መምሪያ እንዲሁ ለሁሉም የ 7ኛ ክፍል ተማሪዎች ሂውማን ፓፒሎማቫይረስ (HPV) የመጀመሪያ ክትባት እዲወስዱ ይፈልጋል፡፡ ወላጅ ወይም አሳዳጊ ልጁ የ HPV ክትባት እንዳይወስድ ከመረጠ ወይም እንደወሰደ ማረጋገጫ ካቀረበ ተማሪው እንዳይካተት አይደረግም፡፡
  • 12 ክፍል የሚገቡ ተማሪዎች የ MenACWY ክትባት በ 11 አመት እድሜ ላይ ቢከተቡም እንኳ እድሜያቸው 16 ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የሆናቸው የሚኒንጎኮካል ኮንጁጌት ክትባት (MenACWY) የሚሰጠውን የማበረታቻ ክትባት ስለመውሰዳቸው ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ተማሪዎች በግል ስለሚኖራቸው መስፈርቶች ወይም ለተማሪው አስፈላጊውን ክትባቶች በአርሊንግተን ካውንቲ የክትባት ክሊኒክ እንዲወስድ ቀጠሮ ለመያዝ ለሚፈልጉ፣ በሚኖራቸው ማናቸውም ጥያቄዎች ላይ እባክዎ የትምህርት ቤት ጤና ክሊኒክ ሰራተኞችን ያግኙ፡፡

More News

Arlington Public Schools to Participate Summer Meals Program

Arlington Public Schools is participating in the Summer Food Service Program. Meals will be provided to students ages 18 and under on a first come, first serve basis, from July 5-Aug. 1 at Carlin Springs Elementary School (5995 5th Road S.).

School Board Meeting June 22, 2023

For closed captions, click the “CC” button in the bottom toolbar of the video window once the meeting starts...

School Board Appoints Principal of Arlington Science Focus Elementary School

At its June 22 meeting, the Arlington School Board appointed Gina Miller as Principal of Arlington Science Focus Elementary School.